የአፍሪካ ሕብረት (አዲስ አበባ)

Ethiopia / Addis Abeba / አዲስ አበባ
 organization (en), ፍላጎትን የሚያሳድር ቦታ
 ምስል ይጫኑ

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (አ.አ.ድ.)፣ በኢትዮጵያ አቆጣጠር፣ ግንቦት 17 ቀን 1955 ዓ.ም፣ ከአፍሪካ የመጀመሪዎቹ የ32 ነፃ አገሮች መሪዎች፣ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ከአፍሪካ አዳራሽ ውስጥ ተሰባስበው ባደረጉት የውል ፊርማ ፀድቆ ተመሠረተ። የድርጅቱም መሪ ከሆኑት ዓላማዎች ውስጥ አንዱ፣ በወቅቱ አንሰራፍቶ የነበረውን የቅኝና የዘርኝነት አገዛዝን ለአንዴም፣ ለሁሌም መገርሰስ ይቻል ዘንድ፣ በአፍሪካ አገሮች መኃከል ትብብር መፍጠር ነበር። የድርጅቱም ዋና መሥሪያ ቤት አዲስ አበባ ይሆን ዘንድ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ያቀረቡት አስተያየት፣ በመስራቾቹ አባላት ዘንድ ተቀባይነትን በማግኘቱ፣ አዲስ አበባ እስከ ዛሬ ድረስ የአፍሪካ ሕብረት ማዕከል ለመሆን በቅታለች።

እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር፣ ሐምሌ 2 ቀን 1994 ዓ.ም፣ የአፍሪካ አንድነት (አ.አ.ድ) በመባል የሚታወቀው ስም ተቀይሮ፣ በአፍሪካ ሕብረት (አ.ሕ.) ተተክቷል። ድርጅቱ 54 አባል አገሮችን ያቀፈ ሲሆን፣ ከሞሮኮ በስተቀር፣ ከአህጉሩ ዋና ምድር ውስጥ በአባልነት ያልተካተተ አገር የለም። አዲሱ የአፍሪካ ሕብረት ማዕከል፣ ዘመናዊ የሆነ ባለ 20 ፎቅ ሕንፃ፣ ትልቅ የስብሰባ አዳራሽ፣ ከተጨማሪ ሕንፃዎች ጋር፣ ጥር 19 ቀን 2004 ዓ.ም (እኢአ) ተመርቆ የተከፈተ ሲሆን፣ መሥሪያ ቤቱ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ፣ ከቦሌ የዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በስተሰሜናዊ ምዕራብ በኩል፣ በ8 ኪሜ (5 ማይል) ርቀት ላይ ይገኛል።
ቀረብ ያሉ ከተማዎች:
መጋጠሚያ፥   9°0'1"N   38°44'38"E
ይህ ዓምድ የመጨረሻው ዕርማት የተደረገበት ከ9 ዓመታት በፊት